መዝገበ ቃላት

በዚህ ገጽ ላይ የግዕዝ ቃላት ከትርጉማቸው ያገኛሉ። ቃላትን በግእዝ ፊደላት ብቻ መድቦ ለማስቀመጥ ሲባል የመጀመርያ ፊደላቸው ከግእዝ ውጭ የሆኑ ቃላትን ከመጀመርያቸው ላይ የግእዝ ፊደል እና የሰረዝ (dash – ) ምልክት ተቀምጧል። ለምሳሌ ሖረ የሚለው ቃል በሳብዕ ፊደል () ስለሚጀምር ከመጀመርያው ሐ- በመጨመር እንደዚህ ተቀምጧል፤ ሐ-ሖረ። ይህም ለአቀማመጥ እንዲመች እንጅ ሐ- በ ሖረ ውስጥ ያለ ፊደል አይደለም። አንባቢዎች ሰረዝ እና ከዚያ በፊት ያለውን ፊደል በመዝለል ቃላትን እንዲያነቡ።

  • ሀ-ህየ

    ህየ= እዚያ ዝየ= እዚህ እምዝየ =ከዚህ እምህየ= ከዚያ እንተ ህየ = በዚያ በኩል እንተ ዝየ = በዚህ በኩል (ወያጸሉ ፡ ህየ ፡ አዕዋፈ ፡ ሰማይ)
  • ሀለወ

    አለ ፤ ኖረ (እስመ ከመዝ ሀለዎ ይኩን/ይህ ይደረግ ዘንድ አለውና)
  • ሀበ

    ሀበ፦ ትርጉም ሰጠ (ክርስቶስ ተንስአ እሙታን ወሀበ ሕይወት / ከርስቶስ ከሙታን ተነሳ ሕይወትንም ሰጠ)
  • ለ-ሊተ

    ለኔ ፤ እኔ ፤ እኔን ፤ ወደኔ ፤ -ልኝ(ብእሲት እንተ ጸሐፈት ሊተ ጦማረ/ደብዳቤ የጻፈችልኝ ሴት ፤ ዝ ቤት ሊተ ውእቱ ዘወሀበኒ አቡየ/ይህ ቤት አባቴ የሰጠኝ ነው ፤ ስምዑኒ ሊተ/እኔን ስሙኝ)። በ፲ መራሕያን፦ ሊተ/ለነ/ለከ/ለኪ/ለክሙ/ለክን/ሎቱ/ላቲ/ሎሙ/ሎን
  • ለሐመ

    ጸና፣ በረታ፣ ከፋ
  • ለምንት

    ለምንት - ለምን ምንት - ምን
  • ለበወ

    ልብ አደረገ አስተዋለ ዐወቀ ኢለበውኩ=አልገባኝም
  • ለፌ ወለፌ

    ወዲህ ወዲያ (ኢትበሉ ለፌ ወለፌ)
  • ሐ-ሖረ

    ሖረ ትርጉም ፦ ሄደ (ኢየሱስ ሆረ እምገሊላ ሀበ ዩሀንስ / ኢየሱስ ከገሊላ ወደ ዮሀንስ ሄደ) ኀበ=ወደ
  • ሐለመ

    አለመ
  • ሐለየ

    አሰበ ፤ ገመተ ፤ መረመረ
  • ሐመ

    ታመመ
  • ሐመለ

    ለቀመ ፤ ለመለመ
  • ሐመመ

    ተመቀኘ
  • ሐሰወ

    ዋሸ (አመንየ ውእቱ ወአኮ ሕሳዌየ/እውነቴን ነው ውሸቴን አይደለም)
  • መ-ሙቃስ

    ወቀሳ
  • መ-ሚ

    ማ ፤ ማን ፤ ምን ፤ ምንኛ ፤ ምን ያህል (ሚ የዐቢ አምላⷈ/አምላኬ ከአንተ ማን ይበልጣል ፤ ሚ ትሤኒ እንተ ወለደታ ሐና/ ሐና የወለደቻት ምን(ኛ) ታምር
  • መ-ምስለ

    ጋር አብሮ (ይመጽእ እግዚእ ፡ ምስለ መላእክቲሁ/ጌታ ከመላእክቱ ጋር ይመጣል)
  • መ-ምዕረ

    አንድ ጊዜ (ምዕረ በዘባነኪ ወምዕረ በገቦኪ ማርያም ብዙኃ በሐዚለ ሕጻን ደከምኪ)
  • መሠጠ

    ነጠቀ ፤ አምሠጠ(አመለጠ) ፤ መሣጢ (ዘራፊ)
Next