10 thoughts on “ስመ ተጸውዖ/Proper Nouns

    1. በአንድ ቋንቋ በንግግርም ሆነ በጽሁፍ የተገለጸን ኃሳብ ለመተርጎም የተነገረውን ወይም የተጻፈውን ኃሳብ መረዳት ይጠይቃል። ለመረዳት ደግሞ መጀመርያ መማር ያስፈልጋል። ሳይማሩ ለመተርጎም መሞክር ወደ ስህተት ከመምራቱም ባሻገር ተስፋ ወደ መቁረጥ ሊመራ ይችላል።
      ወደ ግእዝ ቤተሰብ የሚመጡ ተማሪዎች ዓላማም የማያውቁትን ለማወቅ እና ወደ ተሻለ መረዳት ለመድረስ ነው። በተቻለ መጠን ከቀላል ጀምረን ለማስተማር እንሞክራለን። ተማሪዎች የቃላት ክምችታቸውን በማዳበርና የቋንቋውን ሰዋስው በማጥናት ወደ ተሻለ መረዳት ለመድረስ መጣር ይጠበቅባቸዋል።

      እርስዎም ከመጀመርያው ጀምሮ ትምህርቱን በትእግስትና በዓላማ ካጠኑ ፣ ከድኅረ ገጹ የተማሩትን በቴሌግራም ቻት እየተገኙ ከተለማመዱ በእርግጠኝነት እንነግርዎታለን በአጭር ጊዜ ወደ መረዳት ከዚያም ወደ መተርጎም ብሎም ወደ ንግግር ደረጃ ይደርሳሉ። ለዚህም የቀደሙ ተማሪዎቻችን ምስክሮቻችን ናቸው። የቀደሙ ተማረዎቻችን በጥረት የደረሱበትን ለማየት እዚህ ይጫኑ

      በተረፈ የግእዝ ቋንቋ ከሚታወቁ የኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጋር ስለሚመሳሰልና ስለሚወራረስ ሳይማሩ ወደ ሌላ ቋንቋ ለመተርጎም መሞከር ረጅም ለመሄድ እንቅፋት ይሆናል። ያ ቢሆን ኖሮ መማር ባላስፈለገ ነበር።

  1. በእንተ ጽድቅ አልቦየ ልትናገር አነ ጥቀ እሴብሐከ አቡነ አው እኁየ እዝራ። ፈጣሪ ይሀብልየክሙ ጥዒና አው እድሜ ፀጋ💐🌹🙏🙏🙏

Leave a Reply