በዚህ ገጽ ላይ የግዕዝ ቃላት ከትርጉማቸው ያገኛሉ። ቃላትን በግእዝ ፊደላት ብቻ መድቦ ለማስቀመጥ ሲባል የመጀመርያ ፊደላቸው ከግእዝ ውጭ የሆኑ ቃላትን ከመጀመርያቸው ላይ የግእዝ ፊደል እና የሰረዝ (dash – ) ምልክት ተቀምጧል። ለምሳሌ ሖረ የሚለው ቃል በሳብዕ ፊደል (ሖ) ስለሚጀምር ከመጀመርያው ሐ- በመጨመር እንደዚህ ተቀምጧል፤ ሐ-ሖረ። ይህም ለአቀማመጥ እንዲመች እንጅ ሐ- በ ሖረ ውስጥ ያለ ፊደል አይደለም። አንባቢዎች ሰረዝ እና ከዚያ በፊት ያለውን ፊደል በመዝለል ቃላትን እንዲያነቡ።
-
ጸ-ጽጌ
ጽጌ ማለት = አበባ - ንሕብ ቀሠመት ጽጌ (ንቧ አበባ ቀሠመች) -
ጸሐበ
ሰለቸ ፤ ዘበዘበ -
ጸብአ
ጸብአ - ተጣላ፤ ተዋጋ ጸባኢ - የሚጣላ ፤ ወታደር ጸባኢት - አሸናፊ ጸብእ - ጥል ፤ ጦርነት ጽቡእ - የተሸነፈ ፤ የተወጋ ቁስለኛ (ኢንፃባህ/አንጣላ) ጸብዐ ማለት ግን ቀሰረ ማለት ነው -
ጸነሰ
ተቸገረ ፤ አጣ (እሴብሐከ አልቦ ተጽናስ / አመሰግናለሁ ችግር የለም) -
ጸንሐ
ቆየ ፤ ደጅ ጠና ፤ ታገሰ (ጽንሑ በሰላም) -
ጸዋግ
ክፉ ፤ መጥፎ ፤ ጨካኝ (ኮረና ደዌ ፀዋግ ውእቱ) -
ጸውአ
ጠራ (ዮሐንስሃ ጸውአ ታዴዎስ/ታዴዎስ (ዮሐንስን ጠራ) -
ጸውዐ
ሰጠ (ፍንው ጴጥሮስ ዘተጸውዐ ጸሐፈ መልእክተ/የተጠራው የተላከ ጴጥሮስ መልእክት ጻፈ) -
ጸዐቀ
ተጨነቀ ፤ ተቸገረ (ለምንት ትጸዐቁ ኩልክሙ በእንተ ነገር ኢትክህሉ ባሕቶሙ) -
ጸገወ
ሰጠ ፤ ለገሰ